ጠቃሚ ነጥቦች፣ መሣሪያዎችና ተጨማሪ ሥልጠናዎችን እየፈለጉ ነው? ከታች የሚታዩት መመሪያዎች የምርመራ ጋዜጠኝነት ላይ ያተኮሩ ሲሆን፣ ከተለያዩ የዓለም አገራት የተውጣጡ ተጨባጭ ጥናቶችን እና ምሳሌዎችን ያቀርባሉ። አብዛኞቹ በነጻ የሚገኙ ናቸው፣ ክፍያ አላቸው ተብለው ከተጠቀሱት ውጪ።
Amharic
የምርመራ ጋዜጠኝነት ዘዴዎች ትርጓሜ
|
የምርመራ አዘጋገብን በሚመለከት የተለያዩ ትርጓሜዎች ይሰጡ እንጂ፣ አዘጋገቡ በሚያካትታቸው ነጥቦች ዙሪያ ግን የጋዜጠኝነት ባለሞያዎች ልዩነት የላቸውም። ይልቁንም ሥልታዊ፣ ጥልቀት ያለው፣ ያልተቀዳ ጥናትና ዘገባ፣ ብዙ ጊዜ በምስጢር የተያዙ ጉዳዮችን የሚያጋልጥ ነው በሚለው ላይ ይስማማሉ። ሌሎች ደግሞ ተግባራዊነቱ ላይ የሕዝብ የሆኑ መዝገቦችንና መረጃዎችን በከፍተኛ ደረጃ አካትቶ አትኩሮቱ ማኅበራዊ ፍትህና ተጠያቂነት እንደሆነ አጽንዖት ይሰጣሉ።
Amharic
ጠቃሚ ምክሮች ኮሮና ቫይረስን በተመለከተ ለሚዘግቡ ጋዜጠኞች
|
አዲስ የተከሰተው የኮሮና ቫይረስ የዓለማችን ትልቁ ዜና ሆኖ ቀጥሏል። እንደ ጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ መረጃ እስከ አሁን የኮሮና ቫይረስ ከ167 በላይ የዓለም አገራትን አዳርሶ፣ 11 ሺሕ በላይ ሰዎችን ገድሏል። ከ286 ሺሕ በላይ ሰዎች ደግሞ በበሽታው ተይዘዋል።
Amharic
በአፍሪካ በኮቪድ 19 ዙሪያ የምርመራ ዘገባ ለመሥራት ጠቃሚ ነጥቦች
|
የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎዛ በኮቪድ 19 ዙሪያ የሚወሰዱ እርምጃዎችን በሚመለከት ለኅብረቱ ንግግር ሲያደርጉ፤
Amharic
በአፍሪካ ዓለማቀፍ የምርመራ ዘገባ ኔትወርክ፡ እርዳታ እና ድጋፎች
|
የምርመራ ዘገባ ሥራ ሁልጊዜም ውድ ነው። ዘርፉ በዓለም ደረጃ በከፍተኛ የኢኮኖሚ ጫና ውስጥ በገባበት በዚህ ጊዜ፣ በርካታ የሚባሉ የንግድ//ኮሜርሻል ሚድያዎች ግንዘብን እንደወትሮው ለምርመራ ዘገባ አይመድቡም።
Amharic
በአፍሪካ ዓለማቀፍ የምርመራ ዘገባ ኔትወርክ፡ ፀጥታና ደኅንነት በአፍሪካ
|
በተፈጥሮው፣ የምርመራ ጋዜጠኝነት አደገኛ ሲሆን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ዘጋቢዎችና ኤዲሪተሮችን ስጋት ላይ ይጥላል። ሙሰኛ የሆኑና እጃቸው የዘረመ የመንግሥት ባለሥልጣናት ቆሻሻ የሚያወጡ ጋዜጠኞች ማስፈራሪያዎ ይገጥሟቸዋል። ይህም የምርመራ ሥራውን ለማስቆም የሚድያ ተቋማቸውን እስከመጨረሻው ዝም እስከማሰኘት የሚደርስ ጥረት ነው። እነዚህን ጋዜጠኞች ከደኅንነት እና ፀጥታ ስጋት ለመጠበቅ፣ አንዳንድ የአፍሪካ እና ዓለማቀፍ ድርጅቶች፣ በተመረጡ የአፍሪካ አገራትም ሆነ በመላው አኅጉሪቱ፣ ችግር ላይ ላሉ ምስጢር አጋላጭ ጋዜጠኞች ድጋፍ የሚያቀርቡበትን ፕሮግራም ሠርተዋል።
Amharic
የናይጄሪያው ዓለማቀፍ የምርመራ ዘገባ ማእከል (ICIR) በኮቪድ 19 ምላሽ ተጠሪነትን ለመፍጠር እያደረገ ያለው ግፊት
|
መቀመጫውን በናይጄሪያ ያደረገ ለትርፍ ያተቋቋመው የናይጄሪያ ዓለማቀፍ የምርመራ ዘገባ ማእከል (ICIR)፣ አሁን ላይ ሽፋኑንም አገሪቱ ለኮቪድ 19 እየሰጠች ባለችው ምላሾች ዙሪያ አድርጓል። በዓለማቀፍ የምርመራ ዘገባ ኔትወርክ (GIJN) የአፍሪካ ኤዲተር ከሆነው ከቤኖን ኸርበርት ኦሉካ ጋር ቆይታ ያደረገው ዳዮ አይታን ስለ ቡድኑ እንቅስቃሴ እንዲሁም ለአፍሪካ ስጋት በሆነው ወረርሽኙ ዙሪያ የምርመር ዘገባ መሥራትን በሚመለከት አንስቷል። ዳዮ አይታን የምርመራ ዘጋቢ፣ የዜና ክፍል አማካሪና የሚድያ አሠልጣኝ ነው።
Amharic
የአፍሪካ ዓለማቀፍ የምርመራ ዘገባ ኔትወርክ (GIJN): የሕዝብ መረጃ መዛግብት ተደራሽነት
|
በሰብ ሰሃራ አፍሪካ በሚገኙ በርካታ አገራት፣ አሁን ድረስ መረጃና የሕዝብ የሆኑ የመረጃ መዛግብትን ማግኘት ፈታኝና ከባድ ሥራ ነው። ለምን ቢባል ጋዜጠኞች መረጃ ሲጠይቁ የሚደግፋቸውና የመንግሥት ባለሥልጣናት የሕዝብ የሆኑ መረጃዎችን እንዲሰጡ ግድ የሚላቸው ሕግ አለመኖሩ ነው።